አጠቃላይ እይታ
The Virginia Department of Corrections Citizens’ Academy is a four-week program designed to allow community members to learn more about one of the largest and most complex public safety organizations in the Commonwealth.
የDOC የዜጎች አካዳሚ (Citizens’ Academy) ግልጽነትን ለመጨመር፣ የማህበረሰብ ግንኙነቶችን ለማጠናከር እና በመምሪያው ውስጥ ባሉ የማረሚያ ባለሙያዎች በየቀኑ ስለሚከናወኑ አስፈላጊ ሥራዎች ህዝቡን ለማስተማር የመምሪያውን ቁርጠኝነት ያንፀባርቃል። ይህ ልዩ ተሞክሮ ተሳታፊዎች ስለ ማረሚያ ኦፕሬሽኖች፣ የመልሶ ማቋቋሚያ ፕሮግራሞች፣ የማህበረሰብ ክትትል፣ የአመራር ተግባራት እና የሰራተኛ ልማት ተነሳሽነቶች ጥልቅ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ያደርጋል።
በ 2026 መኸር ወቅት ጀምሮ፣ ፕሮግራሙ በተከታታይ አራት ሳምንታት ረቡዕ ዕለት የሚካሄድ ይሆናል። ተደራሽነትን ለማረጋገጥ፣ የአካዳሚው መገኛ ቦታዎች በእያንዳንዱ አቅርቦት ወቅት በክልሎች መካከል ሊቀያየሩ ይችላሉ።
ለማመልከት
ማን መገኘት ይችላል?
የማኅበረሰብ መሪዎች
የንግድ ሥራ ባለሙያዎች
አስተማሪዎች
በእምነት ላይ የተመሰረቱ ድርጅቶች
የኮሌጅ ተማሪዎች
የሲቪክ ድርጅቶች
በወንጀል ፍትሕ እና በሕዝብ ደኅንነት ላይ ፍላጎት ያላቸው ግለሰቦች
የማረሚያ ባለሙያዎች ቤተሰቦች እና ጓደኞች
የታራሚዎች ቤተሰቦች እና ጓደኞች
መስፈርቶች
ዕድሜያቸው 18 ዓመት ወይም ከዚያ በላይ መሆን አለበት
አራቱንም ክፍለ ጊዜዎች መከታተል መቻል አለባቸው
የቤተሰብ አባል ወይም ወዳጅ የሚገኝበትን ተቋም መጎብኘት አይችሉም
በአሁኑ ጊዜ ክትትል ላይ ያሉ ግለሰቦች እንደየሁኔታው ይታያሉ
ሥርዓተ ትምህርት
-
ሳምንት 1፦ ዋና መሥሪያ ቤት እና ሥራ አስፈፃሚ ኦፕሬሽኖች (5:30 ከሰዓት – 8:00 ከሰዓት)
-
ተሳታፊዎች የሕክምና እና የአእምሮ ጤና ክትትልን፣ የሙያ ደረጃዎችን እና ድርጅታዊ የአመራር መዋቅርን ጨምሮ ስለ ማዕከላዊ ስራዎች እና የስራ አስፈፃሚ አመራር ተግባራት ለመማር ዋና መሥሪያ ቤቱን ይጎበኛሉ።
-
-
ሳምንት 2፦ ከግድግዳው በስተጀርባ (9:00 ከጥዋቱ – 2:00 ከሰዓት በኃላ)
-
ተሳታፊዎች የማረሚያ ቤት ሥራዎችን እና የህዝብ ደኅንነት ተግባራትን በቅርበት የሚመለከቱበት እና የሚሳተፉበት ዕድል ያገኛሉ፤ ይህም የማረሚያ ተቋምን በጉብኝት መመልከትን ይጨምራል። ይህ በይነተገናኝ ልምድ ስለ እስር ቤት አካባቢ፣ ስለ ታራሚዎች ቁጥጥር፣ ስለ መልሶ ማቋቋም ጥረቶች እና ስለ ማረሚያ ቤት ሠራተኞች የሚጠበቅ ሙያዊ ብቃት ግንዛቤን ይሰጣል።
-
-
ሳምንት 3፦ እንደገና ማህበረሰብ መቀላቀል እና የማህበረሰብ ማረሚያዎች (5:30 ከሰዓት – 8:00 ከሰዓት)
-
ተሳታፊዎች ስለ ማህበረሰብ ቁጥጥር፣ የታራሚዎች ወደ ማህበረሰብ የመመለስ ዝግጅት፣ የትምህርት እና የሙያ ስልጠና ፕሮግራሞች፣ እንዲሁም የተሳካ መቀላቀልን ስለሚደግፉ አጋርነቶች የተሻለ ግንዛቤ ለማግኘት የሙከራ ጊዜ እና የአመክሮ ቢሮን ይጎበኛሉ።
-
-
ሳምንት 4፡ የሰራተኞች ልማት አካዳሚ (5:30 ከሰዓት – 8:00 ከሰዓት)
-
የመጨረሻው ሳምንት በአስተዳደር ክፍል ተግባራት ላይ የሚያተኩር ሲሆን፣ የሰው ኃይል፣ የሰራተኛ ስልጠና እና የአመራር ክህሎት ማዳበር፣ የጤና እና ደኅንነት ፕሮግራሞች፣ እንዲሁም የሰራተኛ ድጋፍ አገልግሎቶችን ያካትታል።
አካዳሚው ፕሮግራሙን በተሳካ ሁኔታ ያጠናቀቁ ተሳታፊዎችን እውቅና የሚሰጥ፣ የክብር እንግዶች የሚገኙበት እና የፎቶ እድሎች የሚኖሩበት የምረቃ ስነ-ሥርዓት ይኖረዋል።
-
ያነጋግሩን
ማንኛውም ጥያቄ አለዎት? እኛ ለመርዳት እዚህ እንገኛለን!